ስለ እኛ

መጽሐፍ ቅዱስ በታሪክም ሆነ በትንቢት ይናገረናል፡፡ ከዚህ በፊት የመጣውን እና በቅርቡ የሚከሰተውን ይነግረናል፡፡ በሚያስደንቅ ትንቢት፣ የዓለም ውድመት ከመከሰቱ በፊት የመጨረሻውን የማስጠንቀቂያ መልእክት ማንበብ እንችላለን፡፡

ይህ በራእይ 14 በሦስቱ መላእክት የተብራራው የማስጠንቀቂያ መልእክት በሦስት ክፍሎች ቀርቧል፡፡ እነዚህን እያንዳንዳቸውን ማስጠንቀቂያዎች መላው ዓለም ይሰማቸው ዘንድ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡

  • የመጀመሪያው መልአክ፣ ሰማይን፣ ምድርንና ባሕርን የሠራውን፣ ፈጣሪ እግዚአብሔርን እንድናመልክ ይነግረናል፡፡ የፍርዱ ሰዓት ስለደረሰ ፈጣሪን ማምለክ አለብን፡፡ የመጀመሪያው መልአክ፣ ይህን አምላክ እንዴት ልናውቀው እንደምንችልና በፍርድ ለማለፍ ዝግጁ እንድንሆን ይነግረናል፡፡

  • ሁለተኛው መልአክ፣ በመጨረሻው ዘመን ስለሚከሰተው ኃይማኖታዊ ክህደት ያስጠነቅቀናል፡፡ ፈጣሪ እግዚአብሔርንና የተገለጸውን ቃሉን ከማያከብሩ ኃይማኖታዊ ተቋማት ውጡ ሲል ነግሮናል፡፡

  • ሦስተኛው መልአክ፣ ክፉው፣ በፈጣሪ አምላክና በእርሱ በሕዝቦች ላይ አንድ የመጨረሻ ጥቃት ለማቀነባበር በከሃዲው ኃይማኖታዊ መዋቅር በኩል እንደሚሠራ ያስጠነቅቀናል፡፡ ክፉውን በሚከተሉ ላይ “ምልክት” የሚደረግባቸው ሲሆን፣ ለእግዚአብሔር ታማኝ ሆነው የሚቀጥሉት ደግሞ ስደት ይደርስባቸዋል፡፡ ሆኖም ይህ አስከፊ ምልክት ባለባቸው ላይ እግዚአብሔር ቅጣቶቹን ያወርዳል፡፡ እምነት ያላቸውና የሚታዘዙ ሕዝቦቹ ግን እየሞተች ካለችው ምድር እልቂት ይተርፋሉ፡፡ ወደ ሰማይ ይሄዳሉ፣ ከእግዚአብሔርም ጋር ሆነው እርሱ መጀመሪያ በነበራት ፍጽምናዋ ዓለምን እንደገና ሲፈጥራትም ይመለከታሉ፡፡

የዜና መጽሔታችንን ለማግኘት ይመዝገቡ

አዳዲስ ሕትመቶች ሲወጡ ለማወቅ የመጀመሪያ ይሁኑ

newsletter-cover